ሎት 1 ጨርቅ (ለወንዶች ሙሉ ልብስ እና ለሴቶች ጉርድና ኮት)፣ የቱታ የጋዎን ነጭ ጨርቅ፣ አጭር የቆዳ ጫማ (የሴቶች እና የወንዶች)፣ ሸሚዝ (የሴቶች እና የወንዶች)፣ ፕላስቲክ ቡትስ ጫማ፣ ለጽዳት ሰራተኞች እጅ ጓንት አጭር ጉርድ ውስጥ ልብስ፣
የጨረታ ማስታወቂያ
አሶሳ ግ/ቴ/ሙ/ት/ሥ ኮሌጅ 2019 ዓ/ም ለሰራተኞች ደንብ ልብስ አገልግሎት የሚውል
ሎት 1 ጨርቅ (ለወንዶች ሙሉ ልብስ እና ለሴቶች ጉርድና ኮት)፣ የቱታ የጋዎን ነጭ ጨርቅ፣ አጭር የቆዳ ጫማ (የሴቶች እና የወንዶች)፣ ሸሚዝ (የሴቶች እና የወንዶች)፣ ፕላስቲክ ቡትስ ጫማ፣ ለጽዳት ሰራተኞች እጅ ጓንት አጭር ጉርድ ውስጥ ልብስ፣
ሎት 2 የደንብ ልብስ ስፌት የእጅ ዋጋ የወንዶች ሙሉ ልብስ ከነ ገበር፣ የሴቶች ጉርድና ኮት፣ ጋዎን፣ ሽርጥ ከነቆብ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሠረት በጨረታው መሳተፍ ስምትፈስጉ ተጫራቾች፡-
- ተጫራቾች በዚህ ንግድ ሥራ ዘርፍ ለመስራት የሚያስችላችሁ ህጋዊ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የዘመኑ የ2018/2019 ዓ/ም ግብር የከፈሉ እና በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው እና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት (VAT) የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፣
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን በግልጽ የመወዳደሪያ ከተራ ቁጥር 1-3 የተዘረዘሩት ሠነዶቻችውን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ተከታታይ ቀን 8፡00 ድረስ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን አሶሳ ግ/ቴ/ሙ/ት/ሥ/ኮሌጅ ድረስ በማምጣት ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- የእያንዳንዱ እቃ ዋጋ የሚሞላው ኮሌጁ በሰጠው እስፔስፍኬሽን ዝርዝር ላይ ብቻ ይሆናል።
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ተከታታይ ቀን ልክ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 8፡30 ሰዓት ላይ ጨረታው በግልጽ ይከፈታል። ቀኑ ቀዳሜ እሁድ /በዓል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- የጨረታ ሰነዱ ላይ ስርዝ ድልዝ ወይንም ለመለየት አሻሚ የሆነ ነገር መኖር የለበትም፣
- ሌሎች ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው፣
- ተጫራቾች የጨረታውን ሙሉ ዝርዝር የያዘ ሰነድ ብር 200 የማይመለስ በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ አርብ በተከታታይ 15ኛው ቀን አሶሳ ግብርና ቴ/ሙ/ት/ሥ/ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 6 በመቅረብ መግዛት ይቻላል፣
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚጫረቱበትን ጠቅላላ ዋጋ 2 ፐርሰንት ከታወቀ ባንክ ጋራንቲ ወይንም ሲፒኦ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ከጨረታ ሰነድ ጋር በማስያዝ ማቅረብ ይኖርበታል። 2 ፐርሰንት ሲፒኦ ካላቀረበ ወይም ከ2 ፐርስንት ያነሰ ከሆነ ከውድድሩ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይሰረዛል፣
- ኮሌጁ አሸናፊ ድርጅት የሚመርጠው በእያንዳንዱ ዕቃ ዝቀተኛ ዋጋ እንጂ በጠቅላላው ድምር ዋጋ አይደለም።
- አሸናፊዎች የየውል ማስከበሪያ ያሸነፈበት 10% በማስያዝ ማሸነፉ ከተገለፀላቸው በ5 ቀናት ውስጥ ውል መግባት አለባቸው።
- አሸናፊዎች እቃውን የሚያስረክቡት ለሎት 1፣ ሎት 2 በአሶሳ ግት/ሙ/ት/ሥ/ኮሌጅ ውስጥ ባለው ንብረት ክፍል ይሆናል፣
- ስለጨረታው አጠቃላይ መረጃ ከጨረታ ሰነዱ እና ከተጫራቾች መመሪያ ላይ ማግኘት ይቻላል።
- የጨረታ መዝጊያ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፣
- ተጫራቾች በጨረታው መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባይገኙ የጨረታ ሂደት አይስተጓጉልም፣
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተሰጠው ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- ፌስ ቡክ ገጽ Asosa Agricultural TVET College ወይም በሞባይል ስልክ ቁጥር 0919793058/0911106356/0917176304
የአሶሳ ግ/ቴ/ሙ/ት/ሥ/ኮሌጅ
