Tender Detail

Tender Details


በአቃ/ቃ/ከ/ከ የወረዳ 10 አስተዳደር ለ2019 በጀት ዓመት በስሩ ላሉ ጽ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የግዥ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ መስታወቂያ ቁጥር ፋ/ጽ 002/2019

በአቃ/ቃ/ከ/ከ የወረዳ 10 አስተዳደር ለ2019 በጀት ዓመት በስሩ ላሉ ጽ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

  1. የደንብ ልብስ
  2. አላቂ ቢሮ ዕቃዎች
  3. ህትመት
  4. የፅዳት ዕቃዎች
  5. ሌሎች አለቂ የቢሮ ዕቃዎች
  6. የጓሮ አትክልት
  7. ጥገና(የቢሮ ኤልክትሮኒክስ)

ሎት1፤ CPO 100,000/ አንድ መቶ ሺህ/ ብር፡

ሎት2፤ CPO 40,000/አርባ ሺህ/ ብር፤

ሎት3፤ CPO 100,000/ አንድ መቶ ሺህ/ ብር

ሎት 4፤ CPO 30,000/ ሰላሳ ሺህ/ ብር

ሎት5፤ 50,000/ሃምሳ ሺህ/

ሎት6 CPO 12,000(አስራ ሁለት ሺህ)

ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።

  1. በስራው ዘርፍ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር ከፍለው ንግድ ፍቃዳቸውን ያሳደሱ፡፡
  2. ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢዎች ስለመሆናቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ።
  3. በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ድረ ገጽ በአቅራቢነት ተመስጋቢና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ ከላይ በየሎቱ በተገለጸው የብር መጠን መሰረት አቃ/ቃ/ክ/ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር በምል CPO ማሰራት ይጠበቅባቸዋል።
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሠነድን የማይመለስ ብር 300(ሶስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሠነድ ወረዳ 10 ፋ/ጽ/ቤት በመቅረብ ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት እለት ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰአት ከጠዋት 2፡30 እሰከ 11፡30 ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
  6. በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው ለሚሰሩ ከስራና ክህሎት ጽ/ቤት የትብብር ደብዳቤ በማምጣት በተፈቀደላቸው የስራ ዘርፍ/የሚያመርቱት ምርት/ላይ ብቻ ያለክፍያ የጨረታ ሰነድ መውሰድና የጨረታ ማስከበሪያ ሳያስዙ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ከሚያመርቱት ምርት ውጭ ከሆኑ ዕቃዎች ላይ እንደማንኛውም ነጋዴ የጨረታ ሰነድ መግዛትና CPO ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የሚጫረቱበትን መወዳደሪያ የአንዱን ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ በመሙላት በታሸገ ፖስታ ውስጥ አድርጎ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ ወረዳ 10 ፋ/ጽ/ቤት ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ተዘግቶ ጠዋት 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  8. ተጫራቾች የተወዳደሩበትን የእቃ ናሙና ከየአይነቱ አንዳንድ ብቻ ማቅረብ አለባቸው።
  9. አሸናፊ የጨረታ ተወዳዳሪ ማሸነፉ ከተገለጸለት በኋላ በ5 ቀን ውስጥ ከግዥው ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ አለበት።
  10. አቅራቢው ተጫራች በውሉ መሰረት ግዴታውን ካልተወጣ ለውል ማስከበሪያ ያስያዙት 10% ገንዘብና ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው CPO ሙሉ በሙሉ የሚወረስ ይሆናል።
  11. ተወዳዳሪ ተጫራቾች በጨረታው ሰነድ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር አለባቸው።
  12. የጨረታ ሰነድ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ሆኖ መቅረብ አለበት።
  13. ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻችን፡

  • በአ/ቃ/ ክ/ከ የወ/10 ፋ/ጽ/ቤት ወደ ጎሮ መሄጃ ቀርሳ አደባባይ ከአስፓልት በስተቀኝ ገባ ብሎ

ስልክ ቁጥር፡- 0961 091 86 / 0909 289 281 / 0921 067 960

በአቃ/ቃ/ክ/ከ የወረዳ 10 ፋይናንስ ጽ/ቤት

Save Tender