በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለወረዳው ሴክተር መስሪያ ቤቶች አግልግሎት የሚውል
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለወረዳው ሴክተር መስሪያ ቤቶች አግልግሎት የሚውል
- ሎት 1 ጽ/መሣረያና ሌሎች አላቂ ዕቃዎች ግዥ
- ሎት 2 የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ እና
- ሎት 3 የመኪና ጥገና አግልግሎት ግዥ
በውል የምታሰር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማስጠገን ይፈልጋል። በዚህ መሠረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፦
- በየዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው።
- የዘመኑን የግብር ክፍያ ማረጋገጫ እና TIN ያላቸው።
- የቫት/ተጨማሪ ዕሴት ታክስ ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችል።
- በአቅራቢነት የተመዘገበበትን ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ያሸነፈበትን ዕቃ ዝርዝር በተፈለገበት ጊዜና ሰዓት በራሳቸው ወጪ እስከ ጋጮ ባባ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት ንብረት መጋዘን ማቅረብ የሚችሉ፤ የመኪና ጥገና በራሱ ጋራዥ መጠገን የሚችል።
- አገልግሎት የማይሰጡና የጥራት ችግር ያለባቸውን ዕቃዎች መመለስና መተካት የሚችሉ።
- ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከጋጮ ባባ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት ግዥ ክፍል በመቀረብ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ 300 (ሶስት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
- ጨረታው የሚከፈተው 16ኛው የሥራ ቀን ሲሆን፤ ሎት-1, 3፡00 ሰዓት ታሽጎ 3፡10 ላይ የሚከፈት ሲሆን ሎት-2, 4፡30 ታሽጎ 4፡40 ሰዓት ላይ ይከፈታል። ሎት-3 ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ታሽጎ 8፡10 የሚከፈት ይሆናል። ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል። ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በጨረታ መክፈቻ ላይ ባይገኙ ጨረታውን አያስተጓጉልም።
- ተጫራች በእያንዳንዱ ሎት የጨረታ ማስከበሪያ 50,000 /አምሳ ሺህ ብር/ ብቻ በተመሳሳይ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ የብድ ቦንድ/ የባንክ የክፍያ ማዘዣ ማቅረብ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች ያቀረቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን መግለጽ አለባቸው፤ ካልተገሰጸ ግን ቫትን ያካተተ ተብሎ ይወሰዳል።
- አሸናፊው ድርጅት የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል።
- የጨረታው አሸናፊ የሚለየው በዕቃዎች እያንዳንዱን ዕቃ በዕቃው ዋጋ በማቅረብ ይሆናል።
- ክፍያ የሚፈጸመው ተጫራች ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች በራሱ ትራንስፖርት እስከ መ/ቤቱ ድረስ አቅርቦ የዕቃዎቹ ደረጃ ከተረጋገጠ በሞደል 19 ገቢ ከተደረገ በኋላ ብቻ ይሆናል።
- መ/ቤቱ ሌላ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፦ 0913868795 /0954774308
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጋሞ ዞን የጋጮ ባባ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት
