የሀላባ ዞን የአቶት ኡሎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀላባ ዞን የአቶት ኡሎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- የጽ/መሣሪያ እና ሌሎች አላቂ የጽዳት ዕቃዎች (ሎት1)
- የደንብ ልብስ (ሎት2)
- የሞተር ሣይክል (ሎት-3)
- የኤሌክትሮኒክስ (ሎት 4)
- የፈርኒቸር (ሎት-5) በዚህ መሠረት
- በዘርፉ የተሰማራችሁ የ2017 ዓ/ም የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- የአቅራቢነት እና የግብር ከፋይነት ምስክር ወረቀት ያላቸው
- የቫት ተመዝጋቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 100 ብር በመክፈል ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ግዥ/ፋይ/ንብ⁄ አስ/የስ/ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ 5000 (አምስት ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ CPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን እያንዳንዱን አንድ ኦርጅናል አንድ ኮፒ በማዘጋጀት ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ለዚሁ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቢሮ ቁጥር 01 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ22ኛ ቀን ከጠዋት 5፡00 ሰዓት ታሽጎ 5፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። በዕለቱ ተጫራቾች ያለመገኘታቸው ጽ/ቤቱን ጨረታውን ከመክፈት የሚያግደው ነገር አይኖርም፡፡
- የጨረታው መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች ለወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ከተገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የሀላባ ዞን የአቶት ኡሎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
