Tender Detail

Tender Details


የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት አመት ለወረዳው ጽ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡


የጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2019 በጀት አመት ለወረዳው ጽ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

  • ሎት 1- ስሳቂ አቃዎች
  • ሎት 2- የደንብ ልብስ
  • ሎት 3 - የጽዳት ዕቃዎች
  • ሎት 4–የተሽከርካሪ ጎማዎች
  • ሎት 5- የህትመት አገልግሎት
  • ሎት 6- መስተንግዶ አገልግሎት
  • ሎት 7 -ትራንስፖርት አገልግሎት
  • ሎት 8፦ የቢሮ ሳተራልና ፈርኒቸር ጥገና
  • ሎት 9 -ኤሌክትሮኒክስ ጥገና
  • ሎት 10 ቋሚ እቃዎች
  • ሎት 11፣ የዲኮርና ሞንታርቦ እና ድንኳን ኪራይ

ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ የሚከተሉትን መስፈርቶች አሟልቶ በጨረታው መወዳደር ይችላል፡፡

  1. ከዘርፉ ጋር ተያያዥ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  2. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፡፡
  3. የንግድ ፈቃድ በወጣበት ስም ወይንም ድርጅት የክፍያ አካውንት ቁጥር መኖር አለበት፡፡
  4. የዘመኑን ግብር የከፈለና የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
  5. ጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁት የምናስተናግደው ባመረቱት ምርት ብቻ በመመሪያው መሰረት ይሆናል፡፡
  6. ከ100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በላይ ከተጫረቱ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት የውል ማስረከቢያ ጨረታው ያሸነፈበት መጠን ልክ 10% ማስያዝ አለበት፡፡
  9. ማንኛውም ህጋዊ ተጫራች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት 10 የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 400.00 በመከፈል የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት 2ኛ ፎቅ መውሰድ ይቻላል፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ማለትም ሎት1 (1.5% በብር23,990.00፤ ሎት2 (1.3% በብር 25,989) ፤ ሎት3 (1.2 % በብር 23,990) ፤ ሎት4 (0.5 % በብር 2,000)፤ ሎት5 (0.5 % በብር 30,735)፤ ሎት6 (0.6 % በብር 29,506)፤ ሎት 7 (0.5 % በብር 1,147)፤ ሎት8 (0.5 % በብር 3,074)፤ ሎት9 (0.5% በብር 3,074)፤ ሎት10 (1.6% በብር 31,987) እና ሎት11 (0.5 % በብር 30,735) በሚል pay/order Addis Ketema K/K Weredato F/TS/BET በሚል ስም የተዘጋጀ በባንክ በተረጋገጠ 1 ሲፒኦ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች በሁሉም እቃዎች ምንጩ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤ ሳምፕል ያልቀረበበትን እቃ የማናወዳድር መሆኑን እየገለፅን ሳምፕሉ ጨረታው ከመከፈቱ 3 ቀን በፊት በማዳበሪያ መቅረብ አለበት። ከተጠቀሰው ቀን ዘግይተው የሚመጡ ሳምፕሎች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡
  11. የሚሞሉት ዋጋ ቫት ያካተቱ መሆን አለባቸው፡፡
  12. ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሰረት የሚወዳደሩበት ዋጋ ከላይ የተጠቀሱትን ደጋፊ ሰነዶች 1 ኦርጂናል እና ኮፒ በአንድ ላይ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  13. ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፈ በኋላ ያሸነፈበትን እቃ በወረዳው ፅ/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ /ማቅረብ/ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  14. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በክኛው የስራ ቀን ተዘግቶ በከኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  16. ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ ያሸነፉበትን የጨረታ አይነት ውል አልገባም ቢሉ ዉጪ ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ ውርስ የሚደረግ እና ለተወሰኑ ወራቶች የትኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት እንዳይሳተፉ የሚደረግ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

አድራሻ - አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት አጠና ተራ ከድልድዩ ከፍ ብሎ

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር -011-22-73-98-21 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ-10 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት

Save Tender