በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2018 የበጀት አመት 1ኛ ዙር ለገላን ማስገባት ክ/ከተማ ለመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚውሉ የተለያዩ፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2018 የበጀት አመት 1ኛ ዙር ለገላን ማስገባት ክ/ከተማ ለመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚውሉ የተለያዩ፡
- የጽህፈት መሳሪያ እና የጽዳት ዕቃዎች
- የመኪና እና ማሽነሪ ጎማዎች
- ፈርኒቸር (ቋሚ ዕቃዎች)
- ለቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ የሚያገለግሉ መሣሪያዎች
- ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች (ቋሚ ዕቃዎች)
- የደንብ ልብሶች አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈለልግ እና
- ለክ/ከተማ አገልግሎት የሚውሉ ኮድ-3 አውቶሞቢልና ኮድ-3 ፒካፕ(pik-up) መኪና በጨረታ አወዳድሮ መከራየት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተገለጸውን መመሪያ መረጃዎች በማቅረብ ተጫራቾች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ፍቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- አቅራቢዎች ዝርዝር ተርታ የተመዘገቡና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ምስክር ወረቀት ያለው፣
- ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/Tin/ተመዝጋቢ የሆነ።
- የዘመኑ ግብር የከፈሉበትን ከሊራንስ ማቅረብ ይኖርባችኋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስራ አምስት (15) ተከታታይ የስራ ቀናት እና በስራ ሰዓት ለያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ ብር 2000.00 (ሁለት ሺ) ብር በገላን ክ/ከተማ ገቢዎች ባለስልጣ ጽ/ቤት በመክፈል ሰነዱን ከገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን የዋጋ ማቅረቢያ ዝርዝር (ሰነድ) ዋና እና ኮፒ ለየብቻ በታሽገ ኤንቨሎፕ በፖስታ/ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስራ አምስት (15) ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ በገላን ከ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት ባዘጋጀነው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል።
- ጨረታው በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥን ታሽጎ (ተዘግቶ) ልክ በዚሁ ቀኑ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በገላን ክ/ከተማ ገ /ጽ/ቤት ውስጥ ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል። ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የማይገኙ ከሆነ ጨረታውን ከመክፈት አያግደውም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ /CPO/ ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን አሸናፊነቱ ከተገለፀላቸው በኋላ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን አሸናፊነቱ ከተገለፀላቸው በኋላ ውል ካልፈፀሙና የውል ማስከበሪያ ካላስያዙ የጨረታ ማስከበሪያ ለመንግስት ገቢ ይሆናል ።
- ማንኛውም ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተገለፀው መሰረት የተጫረተበት ዕቃ ናሙና /Sample/ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጹትን ማንኛውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ጨረታውን ትቻለሁ ማለት አይችልም፡፡
- የመወዳደሪያ በጨረታ ሰነዱ በተዘረዘረው መሠረት ተሞልቶ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 4 45 01 82 በመደወል እና በአካል ተገኝቶ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
አድራሻ ፡ በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት ገላን
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት
