የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት መ/ቤቶች የሚሆን የተሽከርካሪ ጎማ ለ1 ዓመት በሚቆይ የማዕቀፍ ግዥ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት መ/ቤቶች የሚሆን የተሽከርካሪ ጎማ ለ1 ዓመት በሚቆይ የማዕቀፍ ግዥ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ፡-
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት፤ የቲን/TIN/ እና የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች የጨረታ ዶክሜንት ሊገዙ ሲመጡ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት የቲን /TIN/ እና የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ኦርጅናሉን እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ አቅርበው እንዲመሳከር የማድረግ ግዴታ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ ዘወትር በስራ ሰዓት ለተከታታይ 15 ቀናት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ የግዥ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000454348471 ግቢ በማድረግ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.አ /C.P.O/ 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ/ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ከልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ የግዥ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ስም በማሰራት ከጨረታው ሰነድ ጋር በማዘጋጀት እያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በመጻፍ በሰም/ሙ/ በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጅናልና ኮፒ በማዘጋጀት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይ ቀናት ባሉ የስራ ቀናት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዘርፍ በመቅረብ ለዚሁ ሥራ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- የጨረታው ሳጥን በ16ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት ከቀኑ 8:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ቢሮ ላይ ይከፈታል፡፡
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል በመክፈቻው ዕለት የተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ያለመገኘት የጨረታ መክፈት ሂደት እያስተጓጉልም።
- መ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝ/ክል/ፋይናንስ ቢሮ
