የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን ለመመዝገብ የወጣ ማስታወቂያ
የሀገር ውስጥ ጨረታ ቁጥር ሙ ሲፋ /26/2018
በ2019 በጀት ዓመት ፋብረካ ግዢ ለሚፈፀምባቸው ግብዓቶች፣ የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን ለመመዝገብ የወጣ ማስታወቂያ በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙ ገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በ2019 በጀት ዓመት ፋብሪካው ግዚ ለሚፈፀምባቸው ግብዓቶች፣ የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን በጨረታ አወዳድሮ መመዝገብ ይፈልጋል፡
ከፋብሪካው ጋር አብሮ ለመሥራት የሚፈልጉ አቅራቢዎች የማይመለስ ብር 575.00 ከነቫቱ በመክፈል የፍላጎት መግለጫ ሰነዱን አዲስ አበባ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ገርጂ አካባቢ የቀድሞው ኢምፔሪያል ሆቴል መዳረሻ ወለል ከሚገኘው የፋብሪካው ግዥ መምሪያ ቢሮ እየቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የፍላጎት መግለጫ ሰነዳቸውን (መሳተፍ የሚፈልጉበትን የአቅርቦት ዘርፍ መግለጫ
ደብዳቤ በመፃፍ) ከተጠቀሱት ዶክመንቶቹ ጋር በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም. ከረፋዱ 3፡30 ሰዓት ድረስ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ የፍላጎት መግለጫቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው በግዥ መምሪያ ቢሮ ለስዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ሰነዱ በዕለቱ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ተሳታፊዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት በግዥ መምሪያ ቢሮ ይከፈታል፡፡
ፋብሪካው ፍላጎቱን በሙስ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አዲስ አበባ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙ ገር ሲሚንቶ ፋብሪካ
