Tender Detail

Tender Details

  • Company በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙ ገር ሲሚንቶ ፋብሪካ
  • Address , Phone:
  • Website
  • Deadline16 Sep 2019, 9:30 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceብር 575.00 (ከነቫቱ)
  • opening dateመስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት
  • Categories Building Materials , Spare Parts , Other

በ2019 በጀት ዓመት ፋብሪካው ግዢ በሚፈጸምባቸው ግብዓቶች፣ የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን በመመዝገብ የወጣ ማስታወቂያ።


የሀገር ውስጥ ጨረታ

ቁጥር ሙሲፋ/24/26/2018

በ2019 በጀት ዓመት ፋብሪካው ግዢ በሚፈጸምባቸው ግብዓቶች፣ የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን በመመዝገብ የወጣ ማስታወቂያ።

በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙግር ሲሚንቶ ፋብሪካ በ2019 በጀት ዓመት ፋብሪካው ግዢ ለሚፈጸምባቸው ግብዓቶች፣ የግንባታ ቁሳቁሶች፣ ሸቀጦች፣ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚችሉ አቅራቢዎችን በጨረታ አወዳድሮ መመዝገብ ይፈልጋል፡፡

ከፋብሪካው ጋር አብሮ ለመሥራት የሚፈልጉ አቅራቢዎች የማይመለስ ብር 575.00 ከነቫቱ በመክፈል የፍላጎት መግለጫ ሰነዱን አዲስ አበባ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ገርጂ አካባቢ የቀድሞው ኢምፔሪያል ሆቴል መዳረሻ ወለል ከሚገኘው የፋብሪካው ግዥ መምሪያ ቢሮ እየቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የፍላጎት መግለጫ ሰነዳቸውን (መሳተፍ የሚፈልጉበትን የአቅርቦት ዘርፍ የሚገልጽ ደብዳቤ በመጻፍ) ከተጠቀሱት ዶክመንቶች ጋር በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡30 ሰዓት ድረስ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ የፍላጎት መግለጫቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው በግዥ መምሪያ ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

ሰነዱ በዕለቱ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ተሳታፊዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት በግዥ መምሪያ ቢሮ ይከፈታል፡፡

ፋብሪካው ፍላጎቱን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አዲስ አበባ

በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ

✨ messages.ai_summary
Suppliers are invited to register to provide inputs, building materials, goods, spare parts, and related services for the Muger Cement Factory's 2019 budget year purchases. Interested parties must submit a sealed expression of interest with required documents.
Save Tender