የምዕራብ ወለጋ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በ 2018 ዓ/ም የተለያዩ ፋርኒቸሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለዞኑ ሴክተር መ/ቤት ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የምዕራብ ወለጋ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በ 2018 ዓ/ም የተለያዩ ፋርኒቸሮች፤ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለዞኑ ሴክተር መ/ቤት ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ እና በተወዳዳሪዎች መመሪያ መሠረት ተጫራቾች ቀርበው እንዲወዳደሩ ተጋብዘዋል፡፡
1. ጥራት ያላቸውን ዕቃዎች ማቅረብ የሚችሉና በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውና የታዳሱ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤
2. በመንግስት ጨረታዎች መሳተፍ የሚያስችል የምዝገባ የምስክር ወረቀት አግባብ ካለው ህጋዊ አካል ማቅረብ የሚችሉ
3. የ2018 ዓ.ም ግብር አጠናቅቀው የከፈሉበትን ማስረጃ (Tax clearance) የሚያቀርቡና ለታክስ ከፋይነት (TIN) የተመዘገቡና ተጨማሪ ታክስ (VAT) ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ የሚያቀርቡ፤
4. ለጨረታ ማስከበሪያ ጠቅላላ ካቀረቡት ዋጋ 2% በተረጋገጠ (CPO) ከማስረጃቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፤
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት የስራ ቀናት ለእንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር (200) በመክፋል የግዥ ክፍል ከመ/ቤቱ (G+1) ምዕራብ ወለጋ ዞን ገንዘብ ፅ/ቤት መግዛት ይችላሉ፤
6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዱን ምዕራብ ወለጋ ዞን ገንዘብና ፅ/ቤት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፤
7. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የዕቃ ዓይነት እንደዚሁም የድርጅቱን ስም በሚያቀርቡት የተለያየ ፖስታ ላይ በአሪጅናሉና በኮፒው ላይ በግልጽ በመጻፍ በድርጅቱ ማህተም እና ፊርማ አስደግፈው ማቅረብ አለባቸው።
8. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናና ፎቶ ኮፒውን በተለያየ ኤንቬሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
9. የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአሥራ ስድስተኛው የስራ ቀን፣ ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ 8፡30 (በስምንት ሰዓት ተኩል) ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
10. ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ ሲሆኑ ዕቃዎቹን በራሳቸው ማጓጓዣ እስከ ገዥው ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ አለባቸው።
11. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0577712547 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፤
12. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የምዕራብ ወለጋ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት
