የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርኘራይዝ የ2016 በጀት ዓመት የሂሳብ ሰነዶችን በተፈቀደላቸው ባለሙያዎች አወዳድሮ ኦዲት ምርመራ ለማስደረግ እንዲሁም የዶሮ መኖ ጥሬ እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርኘራይዝ የ2016 በጀት ዓመት የሂሳብ ሰነዶችን በተፈቀደላቸው ባለሙያዎች አወዳድሮ ኦዲት ምርመራ ለማስደረግ እንዲሁም የዶሮ መኖ ጥሬ እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
- በዘመኑ የታደሰ በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰርቲፊኬት የሚያቀርብ፤
- የጨረታ ሰነዱን ሲሞሉ የተጨማሪ እሴት ታክስ ጨምረው መሙላት የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር የድርጅቱን ስም፣ አድራሻ፣ ማሕተም፣ ፊርማ በማድረግ በሚነበብ መልኩ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ማቅረብ የሚችል፡፡
- የዶሮ መኖ ጥሬ እቃ የብቃት እና የጥራት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ማቅረብ የሚችል፡፡
- የኦዲት አገልግሎት ሥራው የሂሳብ ሰነዶች እና የሽያጭ ሃሳቦችን ለመመርመር መስማማት የሚችል ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማወዳደሪያ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናሉን በፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከ30/2/2017 እስከ 12/03/2017 ዓ.ም ማስገባት ይችላሉ፤
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ሽያጭ እና ገበያ ልማት ደጋፊ የስራ ሂደት በሽያጭ ክፍል ቢሮ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት/ ባይገኙም/ በ12/03/2017 ዓ.ም 4፡30 ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ የዋጋውን 1/አንድ/ ከመቶ በጥሬም ገንዘብም ሆነ በሲፒኦ ማስያዘ ይኖርበታል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የዋጋውን የውል ማስከበሪያ 10% ሲፒአ በጥሬ ገንዘብ አስይዞ ውል መግባት የሚችል፡፡
- መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
ለበለጠ መረጃ 033 351 06 60
የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርኘራይዝ
