የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ቀጥሎ የተጠቀሱትን የቁም ደኖች የባህርዛፍ ግንድ ፤ ፖል፤ ማገዶ እና አጣና ለተለያዩ ኮንስትራክሽን ስራ የሚውል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የቁም ባህርዛፍ ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር OFWLEBB/GuB-1/2019
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ቀጥሎ የተጠቀሱትን የቁም ደኖች የባህርዛፍ ግንድ ፤ ፖል፤ ማገዶ እና አጣና ለተለያዩ ኮንስትራክሽን ስራ የሚውል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ
* የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ አስሼ ባቱ ዲስትሪክት
* የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሴ ቅርንጫፍ ማና አንጌቱ ዲስትሪክት
በመሆኑም
1. የግንዲለ አጠና የእንጨት መሰንጠቂያ ና ተዛማጅ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች እንድሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፣ቫት ተመዘጋቢ የሆኑት ና የንግድ መለያ ቁጥር (Tin number) ያላቸው ተጫራች ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው 200/ሁለት መቶ ብር/ የማይመለስ በመክፈል ባሌ ጎባ መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ሜድስን ፋኩልቲ ፊት ለፊት በሚገኘውየኦሮምያ ደንና ዱር እንስሳትድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በመግዛት በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
2. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጨምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።
3. ጨረታው የሚከፈትበትና የሚዘጋበት ትከክለኛው ቀንና ሰዓት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለፃል።
4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚሆን ካቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
5. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ፡- በስልክ ቁጥር 022-661-1679 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ
