የአዲስ አበባ ቁጥር 2 የመጀ/ደ/ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ሎት.1 የደንብ ልብስ፣ ሎት2.
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር ግ/ጨ/ /01/2019 ዓ/ም
የአዲስ አበባ ቁጥር 2 የመጀ/ደ/ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ሎት.1 የደንብ ልብስ፣ ሎት2. የደንብ ልብስ ስፌት ሎት 3 የፅህፈት መሳሪያዎች ሎት4. ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች ሎት5. የስፖርት ዕቃዎች ሎት6. የፅዳት መሳሪያዎች ሎት7 የትምህርት መሳሪያዎች ሎት8 የህክምና መሳሪዎች ሎት 9 የህትመት መሳሪያዎች ሎት 10 የኤሌክትሪክ እቃዎችና ማሽነሪ ጥገና ሎት 11 የህንጻ መሳሪያዎች ሎት 12 የህንጻ ጥገና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ማሰራት ይፈልጋል
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የምታሟሉ ተጫራቾች፡-
1. በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ የታደሰ የንግድ ፍቃድ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የቫት ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ እና በአቅራቢነት የተመዘገበ መረጃ ማቅረብ የሚችል።
2. ለሚያቀርቧቸው ለእያንዳንዱ ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ የሚችል።
3. ሰነዱ በሌላው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
4. ተጫራቾች ሙሉ ስማቸውን አድራሻቸውን እና ፊርማቸውን በትክክል መግለጽ አለባቸው።
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት1 ብር 13,600/ለሎት 2. ብር 400/ለሎት 3. ብር 5,000/ ለሎት 4. ብር5,000/ ለሎት 5. ብር 2,000/ለሎት 6. ብር 7,000.00/ ለሎት 7. ብር 2,634.68/ ለሎት 8. ብር 1,800.00/ ለሎት 9.ብር 1,000.00/ ለሎት 10. ብር 1,800.00 ለሎት 11 ብር 800.00 ለሎት 12 ብር 3,000.00 በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ የጨረታ ሰነዶች በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ ሙሉ ሰነዱን ማስገባት አለባቸው።
6. ጨረታው የሚያበቃበት ጊዜ በ10ኛው ቀን በ11፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በንጋታው 4፡00 ሰዓት ላይ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ በመንግስት ስራ ሰዓት ለእያንዳንዱ የጨረታ አይነቶች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ዋጋ 200.00 ብር በመክፈል ከት/ቤቱ ከፋይናንስ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
8. ተጫራቾች ውል ከመፈረማቸው በፊት የጨረታ ማስከበሪያ 10% ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
9. አሸናፊ ድርጅቶች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ት/ቤቱ ድረስ ማቅረብ አለባቸው።
10.ት/ቤቱ በጨረታው ከሚቀርቡት እቃዎች 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው።
11.ት/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻችን፡- አዲስ አበባ ቁጥር 2 የመ/ደ/ት/ቤት ጉ/ክ/ከ/ከተማ ወረዳ 09 አባዲና ፖሊስ ጣቢያ ከፍ ብሎ ወደ ሩፋኤል ቤተ-ክርስቲያን መውጫ መንገድ ከሱመያ መሰናዶ አጠገብ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 09 22 49 39 37
የአዲስ አበባ ቁጥር 2 የመጀ/ደ/ት/ቤት
