የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት መ/ቤቶች የሚሆን የተሸከርካሪ ጎማ ለ2 ዓመት በሚቆይ የማዕቀፍ ግዥ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር: ደ/ም/ኢት/ህ/ክ/መ/ፋይ/
ብሮ 001/2019
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ የመንግስት መ/ቤቶች የሚሆን የተሸከርካሪ ጎማ ለ2 ዓመት በሚቆይ የማዕቀፍ ግዥ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ስመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፦
1. በመስኩ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክሰ ምዝገባ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥርእና የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው::
2. ተጫራቾች ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ቢያንስ አንድ ዙር በመስኩ በመንግስት ግዥ ላይ በመሳተፍ በገቡት ውል መሰረት ስለማቅረባቸው የመልካም ሥራ አፈጻጸም ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዋጋ የተሞላበትን ኦሪጅናልና ኮፒ በመለየት ፊርማና የድረጅቱን ማህተም በእያንዳንዱ ገጽ በማሳረፍ እና በፖስታ በማሸግ ጨረታው ይፋ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ድረስ ቦንጋ በሚገኘው የከልሉ ፋይ/ቢሮ ቁጥር 6 ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት የሚችሉ ሲሆን ዘግይቶ የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 700 /ሰባት መቶ ብር/ በኢት/ን/ባንክ የክልሉ ፋይ/ቢሮ አካውንት ቁጥር 1000454348471 ላይ ገቢ በማድረግና ደረሰኙን በማቅረብ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
5. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ይፋ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ለ15 የሥራ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዕለቱ በ4፡30 ላይ ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎች/ በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ይሁን እንጂ የተጫራቾች ያለመገኘት ጨረታውን ከመክፈት አያስቀርም፡፡ 16ኛው ቀን የስራ ቀን ሆኖ ካልተገኘ በሚቀጥለው የመንግስት የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
6. የጨረታ አሸናፊ የሆነ ተጫራች ጎማዎችን በራሱ ወጪ አጓጉዞ በከልል ከላስተር ከተሞች /ቦንጋ፤ ቴፒ፤ ተርጫ እና ሚዛን አማን ከተሞች አስመርምሮ ስለትክክለኛነቱ በማረጋገጥ ማስረከብ አለበት፡፡
7. ጨረታውን ያሸነፈው አቅራቢ የውል ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ውል ዋጋ 10% ማስያዝ አለበት፡፡
8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 400,000 ብር /አራት መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ CPO ማቅረብ አለባቸው፡፡
9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- በጨረታው ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች በስ/ቁር 047331888 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ
