የደቡብ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለወረዳው ሴ/ር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ ከአቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የደቡብ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለወረዳው ሴ/ር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት እግር ተሽከርካሪ ከአቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት በጨረታው ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል፣፣
2. የአቀራቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል /የምትችል
3. የዘመኑን ግብር ክሊራንስ ከግብር መ/ቤት ያቀረበ፡፡
4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ማቅረብ የሚችል /የምትችል።
5. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ እና ኮፒውን አያይዞ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፡፡
6. የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል /የምትችል፡፡
7. ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዶች ጋር የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
8. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በአሃዝ እና በፊደል መግለጽ አለባቸው። በፊደል እና በአሃዝ መካከል ልዩነት ካለው በፈደል የተገለጸው ይወሰዳል።
9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር ሶስት መቶ (300) በመክፈል ከደ/ቤ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 /አስር/ በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፣፣
10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ፋይናንሻል አንድ (1) ኦርጅናል እና ሁለት (2) ኮፒ እንዲሁም ቴክኒካል አንድ (1) ኦርጅናል እና ሁለት (2) ኮፒ ለየብቻ በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
11. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን መግለጽ ይኖርባቸዋል፡፡ ያለበለዚያ ያቀርቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
12. ተጫራቾች በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ ፈርማቸውን እና የድርጅታቸውን ማህተም ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።
13. ተጫራቾች የጨረታ ፖስታውን በደ/ቤ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
14. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ በ15ኛው ቀን ከሰዓቱ 8፡00 ላይ ታሽጎ በዚያው ቀን ከቀኑ 8:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ ይከፈታል፣ እለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- የደ/ቤ/ወ/ፋ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት
ደ/ወርቅ ስልክ፡- 0966886973 / 0910997747/0929241731 በመደወል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
በሸኮ ዞን የደቡብ ቤንች ወረዳ ፋይናንስ/ጽ/ቤት
