የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት በ2018 ዓ.ም በተቋሙ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሊያሰራ ላቀደው የውጭ ካፌ እና የላንድስኬፕ ስራ ለማሠራት ህጋዊ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት በ2018 ዓ.ም በተቋሙ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሊያሰራ ላቀደው የውጭ ካፌ እና የላንድስኬፕ ስራ ለማሠራት ህጋዊ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት
- ደረጃቸው GC-6/BC-6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የስራ ተቋራጮች 2017 ዓ.ም ፈቃዳቸውን ያሳደሱና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ወይም ከሲዳማ ክልል ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ፤
- አስፈላጊውን መስራትና ማጠናቀቅ አለባቸው።
- በሲዳማ ክልል ውስጥ ሶስት (3) እና ከዚያ በላይ ፕሮጀክቶችን ውል ገብተው ግንባታ እያከናወኑ ያሉ እና ያላስረከቡ ስራ ተቋራጮች ይህን የጨረታ ሰነድ መግዛትም ሆነ መወዳደር አይችሉም፡፡
- በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ፕሮጀክቶችን ሠርቶ ለማስረከብ ከአሰሪ እና ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች ጋር ህጋዊ ውል ገብተው በስራ ወቅት ከአሰሪ መስሪያ ቤት ወይም ከአማካሪ መስሪያ ቤት ማንኛውንም ዓይነት የስራ አፈጻጸም ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው የስራ ተቋራጮች የጨረታ ሰነድ መግዛትም ሆነ መወዳደር አይችሉም፡፡
- የስራ ተቋራጮች ለውድድሩ ያቀረቡትን ብቃት (ቴክኒክ) መወዳደሪያ ሰነዶች ዋና (ኦሪጅናል) ሲጠየቁ አቅርበው ማመሳከር አለባቸው፤ ይህ ተጣርቶ ኮፒው ከዋናው ጋር ተመሳክሮ ትክክለኛ ካልሆነ ተቋራጭ ከውድድሩ ውጭ ይሆናል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ /Bid security/ ብር 60,000.00 (ስልሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና (Bank guarantee) ወይም የክፍያ ማዘዣ (cpo) ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችሉ፤
- የስራ ተቋራጮች በተጫራቾች መመሪያ መሠረት ህጋዊ ፈቃዳቸውን እና ተ.አ.ታ (VAT) የተመዘገቡበትን ሰርተፊኬትና ታክስ ክሊራንስ በማቅረብ የጨረታ ዶክመንት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለ21 (ሃያ አንድ) ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ) ብር በሲዳማ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የስራ ተቋራጭች ከጨረታው መዝጊያ ቀን በፊት የግንባታውን ሳይት በራሳቸው ወጪ አይተው ማረጋገጥ አለባቸው።
- የጨረታው ሰነድ በተጫራቾች መመሪያ መሠረት ተሞልቶ የጨረታ ማስከበሪያ (bid bond security) ፋይናንሻል አንድ ዋና (ኦሪጅናል) እና ሁለት ቅጂ (ኮፒ) እንዲሁም ቴክኒካል አንድ ዋና (ኦሪጅናል) እና ሁለት ኮፒ ሰነዶችን በተለያየ ኤንቨሎፕ በሰም በማሸግ ለየብቻቸው ታሽጎ በአንድ ትልቅ ፖስታ ውስጥ በመክተት በሁሉም ዶክመንት ላይ ስምና አድረሻ በመጻፍ ህጋዊ የሆነ ማህተም በመምታት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጀምሮ በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 እስከ 6፡00 ሰዓት በሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግዥ/ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ከቴክኒካል ሰነድ ጋር አብሮ መታሸግ አለበት፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ከቀኑ 6፡00 ላይ ተዘግቶ ከቀኑ 8፡00 ላይ ይከፈታል፤ የተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈት አያግደውም።
- አሠሪው መስሪያ ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡
- አሸናፊው ተጫራች በጨረታ ሰነድ ላይ በተጠቀሰው መሠረት ለቅድመ ክፍያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ላይ ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተገለጸው ቦታና ሰዓት ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ ስ.ቁ 046 212 5584 መደወል ይቻላል፡፡
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት
