የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርፕራይዝ ለ2017 በጀት ዓመት የዶሮ መኖ ጥሬ እቃዎች እና የዶሮ ክትባት /መድኃኒት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርፕራይዝ ለ2017 በጀት ዓመት የዶሮ መኖ ጥሬ እቃዎች እና የዶሮ ክትባት /መድኃኒት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር የድርጅቱን ስም አድራሻ ማሕተም ፊርማ በማድረግ በሚነበብ መልኩ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ማቅረብ የሚችል፣
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን በድርጅቱ ግቢ ውስጥ ሽያጭ እና ገበያ ልማት ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 02 ማግኘት ይቻላል፤
- የዶሮ መኖ ጥሬ እቃ የብቃት እና የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማወዳደሪያ ዋጋ በመሙላት ኦርጅናሉን በፖስታ በማሸግ የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም በማድረግ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከ11/09/2017 እስከ ቀን 22/9/2017 ዓ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፤
- ከላይ በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 የጨረታ ሳጥኑ ታሽጐ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባይገኙም/ በ 22/09/2017 ዓ.ም 4፡30 ይከፈታል፡፡
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ /ማሻሻያ/ ማድረግም ሆነ ራሳቸውን ማግለል እንደማይቻል፣
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ የዋጋውን 1 /አንድ/ ከመቶ በጥሬ ገንዘብም ሆነ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- የእቃው ርከክብ በተመለከተ ኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርፕራይዝ ግቢ ድረስ ማስረከብ የሚችል፣
- ጨረታውን ተወዳድሮ ከሚያሸንፍ አቅራቢ እስከ 20 በመቶ ተጨማሪ ማዘዝም ሆነ ቀንሶ መግዛት ይቻላል፡፡
- የጨረታ አሸናፊ አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የዋጋውን የውል ማስከበሪያ 10% ሲፒኦ /በጥሬ ገንዘብ/ አስይዞ ውል መግባት የሚችል፡፡ በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል መግባት ባይችል ያስያዘው 1 /አንድ/ ከመቶ የሚወርስ መሆኑ፣
- መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 033 351 0660
የኮምቦልቻ ዶሮ ሀብት ልማት ኢንተርፕራይዝ
