በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር ለገላን ክ/ከተማ መንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እስቴሽነሪ፤ ኤሌክትሮኒክስ፤ ፈርኒቸር፣ የመኪና ጎማዎች እና ደንብ ልብስ እቃዎችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት ሁለተኛ ዙር ለገላን ክ/ከተማ መንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እስቴሽነሪ፤ ኤሌክትሮኒክስ፤ ፈርኒቸር፣ የመኪና ጎማዎች እና ደንብ ልብስ እቃዎችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት /መረጃዎች በማቅረብ/ በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል::
- በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- በአቅራቢ ስም ዝርዝር ተርታ የተመዘገቡና ምስክር ወረቀት ያላቸው::
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin/ ተመዝጋቢ የሆነ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒውን ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አሥራ አምስት /15/ ተከታታይ የሥራ ቀናት እና በሥራ ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ ብር 2000.00 /ሁለት ሺህ ብር/ በገላን ክ/ከተማ ገቢዎች ባለሥልጣን ጽ/ቤት በመክፈል ሰነዱን ከገላን ከተማ ገንዘብ ጽሕፈት ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን የዋጋ ማቅረቢያ ዝርዝር/ ሰነድ/ ዋና እና ኮፒ ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ /በፖስታ/ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አሥራ አምስት /15/ ተከታታይ የሥራ ቀናት እና በሥራ ሰዓት በገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት ባዘጋጀነው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥን ታሽጎ ተዘግቶ ልክ በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት ውስጥ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው የማይገኙ ከሆነ ጨረታውን ከመከፈት እያግደውም፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
- ተጫራቶች ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 100,000 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ (CPO) ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን አሸናፊነታቸው ከተገለጸላቸው በኋላ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ ከ10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን አሸናፊነቱ ከተገለጸላቸው በኋላ በተገለጸላቸው ቀን ቀርበው ውል ካልፈጸሙና የውል ማስከበሪያ ካላስያዙ የጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት (CPO) ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጹትን ማንኛውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ጨረታውን ትቻለሁ ማለት አይችሉም፡፡
- የመንግስትን የፋይናንስ ሕግ እና መመሪያን የሚጥስ ማንኛውም ነገር ተቀባይነት የለውም፡፡
- የሚፈለጉ መረጃዎችን በሙሉ ከጨረታው ሰነድ ጋር ማቅረብ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ፡- 011 4 45 01 82 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላል፡፡
አድራሻ ፡- በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት
በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት
