በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2017 የበጀት አመት አገልግሎት የሚውሉ "Chemistry Machine" መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት በ2017 የበጀት አመት አገልግሎት የሚውሉ "Chemistry Machine" መግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት ተጫራቾች ከዚህ በታች ታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት /መረጃዎች በማቅረብ / በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ የምስከር ወረቀት ያላቸው፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፤
- በአቅራቢዎች ስም ዝርዝር የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin/ ተመዝጋቢ የሆነ፤
- የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታው ዝርዝር መግለጫ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስራ አምስት (15) ተከታታይ የስራ ቀናት እና በሥራ ሰዓት ለአንዱ ሰነድ የማይመለስ ብር 1,500.00 (አንድ ሺ አምስት መቶ መቶ ብር) በገላን ክ/ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በመክፈል ሰነዱን ከገላን ክ/ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት መውሰድ ድ ይችላሉ ::
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን የዋጋ ማቅረቢያ ዝርዝር (ሰነድ) ዋና እና ኮፒ ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ /በፖስታ/ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስራ አምስት (15) ተከታተይ የስራ ቀናት እና በሥራ ሰዓት በገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት ባዘጋጀነው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል።
- ጨረታው በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥን ታሽጎ (ተዘግቶ) በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በገላን ከተማ ገ/ጽ/ቤት ውስጥ ይከፈታል። ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የማይገኙ ከሆነ ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም። ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 70,000.00 (ሰባ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ /CPO/ ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች የጨረታ አሸናፊነታቸው ከተገለፀላቸው በኋላ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይጠበቅባቸዋል::
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጹትን ማንኛውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ጨረታውን ትቻለው ማለት አይችልም፡፡
- የመንግስትን የፋይናንስ ግዥ እና መመሪያን የሚጥስ ማንኛውም ነገር ተቀባይነት የለውም
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር- 0114450182 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
አድራሻ :- በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት
በሸገር ከተማ አስተዳደር የገላን ክ/ከተማ ገ/ጽ/ቤት
