የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2017 በጀት አመት የሚያገለግል የኤች ዲ ፒ ትቦ ሲ ኣይ/ ዲ ሲ ኣይ ጂ ኣይ/ሲ ኣይ እና ኤች ዲ ፒ መገጣጠሚያ (ፊቲንግ) በግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2017 በጀት አመት የሚያገለግል የኤች ዲ ፒ ትቦ ሲ ኣይ/ ዲ ሲ ኣይ ጂ ኣይ/ሲ ኣይ እና ኤች ዲ ፒ መገጣጠሚያ (ፊቲንግ) በግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል።
- የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው፣
- ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ፣
- የጨረታው ዶክመንት የማይመለስ 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክመንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር G1-02 መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታውን ዶክመንት ማስገባት የሚቻለው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2017 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው የሚዘጋው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን 2017 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣ እሁድ ወይ ህዝባዊ በአል ከሆነ ደግሞ ቀጥሎ ባለው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ።
- ሁሉም ተጫራቾች 120,000.00 /አንድ መቶ ሃያ ሺህ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ እና በባንክ የተረጋገጠ ሌተርኦፍ ክረዲት ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት፣ በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው፡፡
- በዶከሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ቀባይነት የለውም፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክመንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል፤
- በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛበት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግስት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ፤
- ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክመንት ተቀባይነት የለውም።
- ጨረታ ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ40 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።
- ጽ/ቤቱ ጨረታውን እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የሚቀርበው ጨረታ ዶክመንት
- ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም፤
- ፋይናንሺያል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።
- ፅ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ፡- ትግራይ መቐለ
ስልክ ቁጥር ፡- 034-44-07-335/09-14-75-58-45
መቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት
