የሰንዳፋ በኬ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ፣ የማያገለግሉ አገልግሎት ድርጅት የማያገለግሉ ኬብሉ የመኪና ጎማዎች እና የማያገለግሉ ብረታ ብረቶችን አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የሰንዳፋ በኬ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ፣ የማያገለግሉ አገልግሎት ድርጅት የማያገለግሉ ኬብሉ የመኪና ጎማዎች እና የማያገለግሉ ብረታ ብረቶችን አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
- የመስሪያ ቤት አድራሻ- ሰንዳፋ በኬ ከተማ አስተዳደር ዳሽን ባንከ ፊት ለፊት በሰንዳፋ በኬ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት በመቅረብ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል የጨረታ ሠነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚቻለው ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2:30-6:30 እና ከሰዓት 7:30-11:00 ሰዓት ብቻ ነው::
- የንብረቶቹን ሁኔታ እስከ ህዳር 12/2017 ዓ.ም ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2:30-6:30 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ ከ7፡30-11፡00 ሰዓት ድረስ በጨረታ ሠነዱ ላይ በተገለጸው ቦታ በመገኘት ማየት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ህዳር 13/2017 ዓ.ም በሰንዳፋ በኬ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ቢሮ ቁጥር 4 ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ህዳር 13/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4:30 ተዘግቶ በዕለቱ በ4፡45 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ጨረታ መነሻ ዋጋ 1% የጨረታ ማስከበሪያ C.P.O በማዘጋጀትና ዋጋ ማቅረቢያው ኤንቨሎፕ ውስጥ በመክተት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የሰንዳፋ በኬ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
